+251-993-818276 akofeda@gmail.com Addis Ababa, Ethiopia

ሲዖልን መሸጋገሪያ

ሁሉን ከምትሰለቅጠው ሲዖል በመስቀሉ ሰውን ወደ ሕይወት ያወጣው የጥበበኛው አናጺ ልጅ እነሆ፡፡ በዛፍ ምክንያት ወደ ሲዖል የወረደው የሰው ልጅ በዛፍ ምክንያት ወደ ሕይወት ተሻገረ፡፡ ከፍጥረቱ ጋር ተቃርኖ እንደሌለው እናውቅ ዘንድ መራራነትን ከቀመስንባት ዛፍ ጥፍጥናንም ቀመስን፡፡ ነፍሳት ከሲዖል ወጥተው ወደ ሕይወት ይሻገሩ ዘንድ መስቀልህን በሞት ላይ ለሰቀልክልን ለአንተ ክብር ምስጋና ይድረስህ፡፡

Holy Cross

አማንያንም፣ ኢኣማንያንም የተሰናከሉበትን የጣዖት አምልኮ በመስቀልክ ላስወገድክ ላንተ ክብር ይገባሃል፡፡ ሕይወት መስሏቸው ወደ አዘቅት የወረዱትን፣ ወደ እውነተኛው ሕይወት ለመለስክ፣ የሕይወት መድሐኒት ለሆንከው ለአንተ ምስጋና ይገባሃል፡፡ ጠፍተው የተገኙቱ ያመሰግኑሃል፤ የጠፉትን በማግኘትህም፣ ያልጠፉት እና ሁሌም የሚኖሩቱን መላዕክት ደስ አሰኘሃቸው፡፡ በሰላምህ በመካከል የነበረውን ጠላትነት አስወግደህላቸዋልና ያልተገዘሩቱ ያመሰግኑሃል፡፡ ውጭያዊ ምልክት የሆነውን እና ያንተ የሆኑት ያንተ ለመሆናቸው የሚለዩበትን ግዝረት በሥጋህ ተቀብልክ፡፡ የተገዘሩቱ በመገዘራቸው ብቻ ያንተ እንዳልሆኑ ይታወቅ ዘንድ የልብ መገዘርን ምልክት አድርገህ ሰጠኸን፡፡ ያንተ ወደ ሆኑት መጣህ፣ እነርሱ ግን አልተቀበሉህም (ዮሐ 1፡11)፣ ያአንተ ያልሆኑቱ ግን ከልጆች የተረፈውን ፍርፋሪ ታበላቸው ዘንድ በኋላህ ያለቅሳሉ፡፡

በቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

ምንጭ፡ The Fathers of the Church Patristic Series 91

Please follow and like us:
error0
fb-share-icon20

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Post

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

የ፳፻፲፭ ዐቢይ ጾምን ምክንያት በማድረግ ያስተላለፉት መልእክት! • በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት እንዲሁም ኢትዮጵውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ! እንደ ስሑትና ደካማ ሰብአዊ ባሕርያችን ሳይሆን

የቤተክርስቲያን አገልጋዮች እና የመንግስት ባለስልጣናት ግንኙነት

በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ከስነ ምግባር ጉድለት እና ከእምነት ጋር በተያያዘ ለረዥም ጊዜ ከባለስልጣናት ጋር ሲታገል ኖሯል፡፡ ከመንግስት ጋር መሞዳመድ የሚባል ነገርንም አያውቅም፡፡ በተለይ በቁስጥንጥንያ እያለ አብዝቶ ስለነዚህ

ኮሮና ቫይረስን አስመልክቶ የፓትሪያርኩ መልዕክት

በተዋረድ ያላችሁ ወንድሞቼ እና በጌታ የተወደዳችሁ ልጆቼ የታላላቅ ከተሞች እምብርት ከሆነችው ከተማ፣ የታላቋ ቤተክርስቲያን የሃጊያ ሶፍያ**** መገኛ ከሆነችው ከተማ፣ በዓለም ላይ ቀድሞ ባማይታወቅ መልኩ እንደ ሰው ልጆች የገጠመንን መከራ እና